በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።
በኢ/ኦ/ቤተክርስቲያን በሃዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት በአንሌሞ ወረዳ የኤንጦ ላፍቶ ሌንቃ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ውስጥ ቤተክርስቲያናቸው በኢ-አማንያን ተቃጥሎባቸው ለ 36 ዓመታት በዛፍ ስር በመሰብሰብና ስዕለ መድኃኔዓለም በማኖር ስርዓተ አምልኮ እየፈጸሙ ላሉት ምዕመናን የተጀመረውን ቤተክርስቲያን በፈቃደ እግዚአብሔር ከፍጻሜ ደርሶ ሚያዝያ 26 ቀን ይመረቃል፡፡ ቅዱስ እንጦንስ መንፈሳዊ የአገልግሎት ማህበር ሚያዝያ 25 ቀን 2006 ዓ.ም. ጉዞ አዘጋጅቶአል። በዚህም ጉዞ እርስዎም የበረከቱ ተካፋይ እንድትሆኑ መድኃኔዓለም ስም ጥሪያችንን እናቀርባለን።
መነሻ ቀን፡ ሚያዝያ 25
መነሻ ሰዓት፡ ከቀኑ 8 ሰዓት
መነሻ ቦታ፡ መናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን በእሳት አደጋ በኩል (ሰሜን በር)
የጉዞ ዋጋ፡ 250.00 ብር ከሙሉ መስተንግዶ ጋር
ለበለጠ መረጃ፡ 0911 53 41 97
0911 14 36 53
0930 10 05 81
0911 80 34 35
0911 92 18 30
0910 01 60 08
0911 16 96 68
No comments:
Post a Comment