Saturday, November 17, 2012

ቅዱስ እንጦንስ

የበረሃዉ መልአክ ቅዱስ እንጦንስ
በተ/ሥላሴ ጸጋ ኪሮስ




እንደተለመደው የኦሪት ዘፍጥረትን ትርጓሜ መሠረት ያደረገውን ተከታታይ ትምህርት ለመማር በማኅበረ ቅዱሳን ሕንጻ ውስጥ ካሉት አዳራሾች በአንዱ ተሰብስበናል፡፡ ትምህርቱ ከመጀመሩ በፊት በወረቀት ለሚጠየቁት ጥያቄዎች የሚሰጡት መልሶች ሁላችንም ስለሚያጓጓን በመጠባበቅ ተቀምጠናል። ከመምህራችን የቀረበው የዕለቱ ጥያቄ ግን ሌላ ነበር። «ዛሬ ቀኑ ስንት ነውየሚል፡፡ ጥር 22 በማለት መለስን፡፡ «ዛሬ የዕለቱ መታሰቢያነት ለማን ነውቀጥሎ ጠየቀን፡፡ መቼም ቅዱስ ዑራኤል መሆኑን አያጣውም፣ ግን ለምን ጠየቀን? በአእምሮዬ የሚመላለስ ጥያቄ ነበር፡፡ ለነገሩ ዕለቱ የተለየ ነገር ቢኖረው ነው እንጂ አይጠይቀንም ነበር፡፡ ይሄን እያሰብኩኝ ዝምታ በሰፈነበት፥ አንድ ልጅ እጁን አነሳና «የመልአኩ የቅዱስ ዑራኤል በዓል ነው» በማለት መለሰ፡፡ መምህራችንም ጥሩ ነው በማለት ተናገረና «ሌላስአለ በተረጋጋ አንደበት፡፡ ከዚህ በላይ እንኳን የማውቀው ነገር የለም አልኩኝ ለራሴ፡፡

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክ በከንባታ ሃዲያ እና ጉራጌ ሀገረ ስብከት ማኅበረ እንጦንስ ማኅበረ እንጦንስ በኢ.ኦ.ተ.ቤ.ክ

ይህ ስዕል , በሃዲያ ዞን ላፍቶ ሌንቃ ከ አ.አ.210 ኪ.ሜ. ርቀት ላይ , በ 1971 ዓ.ም. በአህዛብ ቤተክርስቲያናቸው ተቃጥሎባቸው ከዛን ጊዜ ጀምሮ እስካሁን ድረስ ከላይ በሚታየው መልኩ ዛፍ ስር ስዕል በማኖር ስርዓተ አምልኮ የሚፈጽሙበት ቦታ ነው :: ይህንንም ለ 32 ዓመታት ሙሉ ተቃጥሎ ያልተሰራውን ቤ/ክ መልሶ ለማነጽ እና ለማደረጀት ማኅበራችን በእንቅስቃሴ ላይ ይገኛል :እግዚአብሔር መጨረሻውን ያሳየን , አያርቅብን አሜን

የተቃጠለበት መቅደሱ ላይ የበቀለች የሾላ ዛፍ


በ 1971 ዓ.ም. የቀድሞው ቤ/ክ ከተቃጠለ በውኃላ የተቃጠለበት መቅደሱ ላይ የበቀለች የሾላ ዛፍ (ክረምትና በጋ ከሌሎች ዛፎች ሁሉ የተለየ ልምላሜ ያላት

ቅዱስ እንጦንስ መንፈሳዊ የአገልግሎት ማኅበር

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክ በከንባታ ሃዲያ እና ጉራጌ ሀገረ ስብከት ማኅበረ እንጦንስ

ማኅበረ እንጦንስ በኢ.... ደንብና ሥርዓት መሠረት በከንባታ ሃዲያና ጉራጌ ሀገረ ስብከት አማካኝነት የተቋቋመ ሲሆን በተለይ ከሀገራችን የገጠር ክልሎች ውስጥ በከንባታ ሃዲያ እና ጉራጌ ሀገረ ስብከት ላይ በማተኮር በተለያዩ ምክንያቶች ተዘግተውና ተዳክመው የሚገኙትን አብያተ ክርስቲያናት መልሶ ለማቋቋም፣ የማኅበሩ የቅርብ ጊዜ ዓላማ አስመልክቶ በመጀመሪያ ደረጃ በሃዲያ ዞን የሚገኙ ክርስቲያኖች የተሟላ የወንጌል አገልግሎት የሚያገኙበትን መንገድ ለመፍጠር፣ ከተመፅዋችነት አላቆ ራስን የሚያስችል የልማት መዋቅር ለመዘርጋትና እንዲሁም የሚደርስባቸውን ተፅዕኖ ተቋቁመው በሃይማኖታቸው ፀንተው እንዲቆዩ ለማስቻል የተቋቋመ ማኅበር ነው፡፡