Tuesday, April 2, 2013

ጉዞ ወደ ላፍቶ ሌንቃ መድሐኔዓለም መጋቢት 22 ቀን በተሳካ ሆኔታ አደረገ፡፡

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ! 
የተሳካ መንፈሳዊ ጉዞ 
“የሰማይ አምላክ ያከናውንልናል፥ እኛም ባሪያዎቹ ተነሥተን እንሠራለን” ነህ.2፡20
 በመጀመርያ ይህን ሁሉ ላደረገ ልዑል እግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይግባው እንላለን!! የቅዱስ እንጦንስ መንፈሳዊ የአገልግሎት ማህበር ጉዞ ወደ ላፍቶ ሌንቃ መድሐኔዓለም መጋቢት 22 ቀን በተሳካ ሆኔታ አደረገ፡፡ በጉዞው ለተሳተፉ መንፈሳዊ ወንድሞች ፤ እህቶች ፤ እናቶች ፤ አባቶች ፤ህፃናት በጠቅላላ በማህበራችን ስም ምስጋናችንን እያቀረብን በጉዞው ላይ ከተነሱ ፎቶግራፎች ውስጥ የተወሰነውን አፕሎድ አድርገናል ይመልከቱአቸው ፡፡ የመድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን እዚህ ደርሷል የቀረው የፊኒሺንግ ሥራ ነው፡፡ የመድኃኔዓለምን ቤተ ክርስቲያን በእቃዎችም ሆነ በገንዘብ እንዲሁም በቦታው በመሄድ አገልግሎት በመስጠት ከበረከቱ ተሳታፊ መሆን የምትፈልጉ: የባንክ አካውንት ቁጥር 1000017080249 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መርካቶ፤ ቦንብ ተራ ቅርንጫፍ ቤተክርስቲያኗን በመርዳት በተጨማሪም በየትኛውም ቦታ ያለን ምዕመናን ሁሉ በፀሎት፣ በጉልበት፣ ጥሬ ዕቃ በማቅረብ፣ የበኩላችንን እንድንወጣ መንፈሣዊ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡ ለተጨማሪ መረጃ በእነዚህ ስልክ ደውሉ ፡ +251911 14 36 53 +251911 24 90 37 +251911 53 41 97 +251910 01 60 08 ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር አሜን !

ቤተ ክርስትያናቸው በአሕዛብ ሲቃጠል ለ34 ዓመታት ይህል በዋርካ ስር የምናየውን ስእለ አድህኖ ይዘው አምላካቸውን ሲያመልኩበት እስከዚች ሰዓት ቆይተዋል

No comments:

Post a Comment